(ቀን ታህሳስ 26/2016 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የቀዳማይ ልጅነት ጉዳዮች ትግበራ ዳይሬቶሬት ሰብአዊ መብት ፅንሰ ሃሳብን ከሴቶች መብት አንፃር የሚቃኝ ስልጠና ለሰራተኞች ሰጠ ::
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ በመጡ አቃቢ ሕግ ወ/ሮ ሰላማዊት በላቸው የሰብአዊ መብቶች ከሴቶች መብት ምንነት አንፃር እንዲሁም ማህበረሰቡ በሴቶች ላይ የሚደርሱ ፆታዊ ጥቃቶችን በማጋለጥ ጥቃት የደረሰባቸውን ሰዎች መብት በማስከበር ራሱንና ሴቶችን ከጥቃት ለመከላከል የሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ አስጨብጠዋል ::
0 Comments