ወቅታዊ ዜናዎች

የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገራቀፍ ፈተና የመቁረጫ ነጥብ ማሳወቂያ!

የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና  ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡትን ከግምት ውስጥ በማስገባት እና በተመሳሳይ ሁኔታ ፈተናው የተሰጠበትን አግባብ እና ሌሎች ጉዳዮችን ከግምት በመውሰድ ለአንድ ጊዜ ብቻ  የሚያገለግል የአቅም ማሻሻያ...

read more

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የተመዘገበው ውጤት የተሻለ መሆኑ ተመላከተ፡፡

በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 896,520 ተማሪዎች መካከል፡-  1.  50 ከመቶ እና በላይ  ውጤት ያመጡ ተማሪዎች 3.3 በመቶ ሲሆኑ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 19.8 ፐርሰንት ተማሪዎች 50 እና በላይ ማለፊያ ውጤት ማስመዝገብ መቻላቸው፤ 2.   በሀገር አቀፍ ደረጃ 600 እና በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች...

read more

በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 896 ሺህ 520 ተማሪዎች መካከል ከ50 በመቶ በላይ ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር 29 ሺህ 909 ተማሪዎች መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

የ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ላይ ሪፖርትና ዋና ዋና ግኝቶች በትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ ተሰጥቷል። የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ የፈተና አሰጣጡ ከዚህ ቀደም ከነበሩት የተለየ እንደነበርና በሁሉም የሚመለከታቸው አካል ርብርብ በስኬት የተጠናቀቀ እንደነበር አንስተዋል። በፈተና ወቅትም ምንም አይነት ስርቆት ሳይደረግ የተጠናቀቀ ሲሆን አሁን የተለቀቀው ውጤትም በፈተና ወቅት ሲኮርጁ የነበሩ...

read more

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚከሰቱ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላል የሚያስችል ስልጠና ሰጠ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ከUnicef ጋር በመተባበር ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚከሰቱ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላል የሚያስችል ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በስልጠናው የመድኃኒዓለም አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የአይሲቲና እንግሊዘኛ ቋንቋ መምህራን የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናውን መውሰዳቸው መምህራኑ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚደርሱ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል...

read more

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ላይ ፈተናዉን ለማስተግበር ከተቋቋመዉ ኮማንድ ፖስት አባላት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

ቀን 27/1/2015 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ላይ ፈተናዉን ለማስተግበር ከተቋቋመዉ ኮማንድ ፖስት አባላት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡ ውይይቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ የመሩት ሲሆን በውይይቱ የቢሮው ማኔጅመንት አባላት ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና የትራፊክ ጽህፈት ቤት አመራረችን ጨምሮ...

read more

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በሚሰጥባቸው የፈተና ጣቢያዎች የመስክ ምልከታ ተካሄደ።

ቀን 27/1/2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በሚሰጥባቸው የፈተና ጣቢያዎች የመስክ ምልከታ ተካሄደ። የመስክ ምልከታው በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ላም በረት አከባቢ በሚገኘው የኢፌድሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲቲዩትና በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተካሄደ ሲሆን የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ...

read more
ድጋሚ የትምህርት ማስረጃ

ድጋሚ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ አገልግሎት ለማግኝት መሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች፡-

  • ማንነትን የሚገልጽ ህጋዊ መታወቂያ ይዞ መቅረብ
  • ባለሙያው የሚሰጠውን ቅጽ መሙላት
  • ከአንድ ዓመት ወዲህ የተነሱትን 3×4 የሆነ ፎቶ ግራፍ
  • ጠያቂው ወይም ህጋዊ ወኪል በአካል መቅረብ ይገባዋል
  • ከላይ የተገለጹት ቅድመ ሁኔታዎች ከተሟሉ 100.00 ብር በመክፈል አገልግሎቱን ማግኘት ይቻላል
የአቻ ግመታ አገልግሎት

የአቻ ግመታ አገልግሎት ለማግኘት መሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች :-

  • የትምህርት መረጃውን በተማሩበት አገር የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቦርድ ወይም District of education /council/ በጀርባው ላይ የባለስልጣኑ ስም፣ ቲተርና ማህተም እንዲሁም በተማሩበት ሀገር ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማህተምና ፊርማ የተረጋገጠ መሆን አለበት
  • የትምህርት መረጃው ከእንግሊዘኛ ቋንቋ ውጪ የተጻፈ ከሆነ በኢትዮጵያ ህጋዊ መተርጎም ፈቃድ ባላቸው ድርጅቶች የተተረጎመና በተርጓሚው ድርጅት ማህተም የተረጋገጠ መሆን ይገባዋል ፡፡
  • በትምህርት መረጃው የፈተና ውጤቶች በፊደል ወይም በቁጥር ከተሰጡ ምን ማለት እንደሆነ አቻ መገለጫ ያለው መሆን አለበት
  • የትምህርት መረጃና የሌሎች ማስረጃዎች ዋናና አንዳንድ ፎቶ ኮፒ መቅረብ አለበት
  • መረጃ ጠያቂው ወይም ህጋዊ ወኪል በአካል መቅረብ ይኖርበታል
  • ከላይ የተገለጹት ቅድመ ሁኔታዎች ከተሟሉ 50.00 ብር በመክፈል አገልግሎቱን ማግኘት ይቻላል ፡፡
የተቋማት ጥራት ኦዲት

ተቋማት የጥራት ኦዲት እንዲደረግላቸው የሚከተሉት ቅድመ ሁኔታዎች ይጠበቁባቸዋል፡-

  • በተላከላቸው ቅጽ መሠረት የውስጥ ግምገማ ያደረጉበት ሪፖርት፣
  • ተቋሙ እውቅና/የዕድሳት የፈቃድ ማረጋገጫ
  • የተቋሙ ስም የትምህርት ደረጃ/መስክ
የትምህርት ቤት ስታንዳርድ

ትምህርት ለሁሉም!

ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም በትምህርት ዘርፍ ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ ቢሮዉ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ፕሮጄክቶችን በመቅረጽ በቢሮዉ አንዲሁም  በከተማዉ ዉስጥ በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃና የመሰናዶ ትቤቶች ዉስጥ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡

agsdi-book

ዲጂታል ት/ቤቶች

በከተማዋ የሚገኙ ሁሉንም የሁለተኛ ደረጃና የመሰናዶ ትቤቶችን በኔትዎርክ በማገናኘት የበይነ-መረብ የመስመር ላይ ት/ትና የተለያዩ ግብዓቶችን በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ዘመናዊ ኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ ነዉ፡፡

agsdi-refresh

የERP ሲስተም

በከተማዉ የትምህርት ቢሮ ዉስጥ የሚገኙ የተለያዩ ክፍሎችን የሥራ መረጃዎችንና የተለያዩ ግብዓቶችን መረጃ መዝግቦ ለመያዝና ለመቆጣጠር የሚያስችል አፕልኬሽን ነዉ፡፡

agsdi-file-check

የፈተና ባንክ

ለተማሪዎች በአንድ ቦታ የተከማቹ የየክፍላቸዉን የተለያዩ የትምህርት ዓይነት የመልመጃ ፈተናዎችን የያዘ ሲስተም ሲሆን፤ትክክለኛዉ የጥያቄዉ መልስ የትኛዉ አንደሆነ እዛዉ ሲስተም ላይ ማወቅ የሚችሉበት ነዉ፡፡

agsdi-mobile

የአንድሮይድ አፕ

ለተማሪዎችና ለመምህራን የሚያገለግሉ መፅሀፍትንና የኦንላይን ፈተናዎችን እንዲሁም የተለያዩ ጠቃሚ ግብዓቶችንና አገልግሎትችን የያዘ የአንድሮይድ ስልክ መተግበሪያ ነዉ፡፡

የስኩል ኔት ዋናዉ ዳታ ሴንተር

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2014 ዓ.ም የተማሪዎች እና የተቋማት መረጃ (የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ)

የ2014 ዓ.ም ጠቅላላ የተማሪ ብዛት

የ2014 ዓ.ም የት/ት ተቋማት ብዛት