“በትምህርት ቤት ላይ በሚከናወኑ የዘርፈ ብዙ ኤች አይቪ / ኤድስ መርሀ-ግብሮች ” ላይ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰልጠና ተሰጠ::

by | ዜና

(ቀን ታህሳስ 20/2016 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘርፈ ብዙና ቀዳማይ ልጅነት ትምህርት ትግበራ ዳይሬክቶሬት የኤች አይቪ/ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ለ4  ለአራዳ፣ ለአዲስ ከተማ ፣ ለቂርቆስና ለጉለሌ ክፍለ ከተሞች ለመጡ የመንግስት ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ መምህራን እና ለጤና አጠባበቅ ክበብ ተጠሪ መምህራን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰልጠና ሰጠ::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘርፈ ብዙና ቀዳማይ ልጅነት ትምህርት ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ በላይነሽ የሻው በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ላይ ኢንዳሉት ማህበረሰቡ በኤች አይቪ/ ኤድስ  ስርጭት ላይ ያለው አመለካከት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ የመጣ በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስቧል።

ስልጠናው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ባለሙያ  ወ/ሮ ትዕግስት መንገሻ የተሰጠ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘርፉ ባለሙያ የሆኑት ገንዘብ ደሳለኝ በወቅታዊ የኤች አይቪ/ ኤድስ ሰርጭት ፣ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የመከላከል እና የመቆጣጠር ስራዎች የተመዘገቡ ውጤቶች፣ የኤች አይቪ  አጋላጭ እና ተጋላጭነት ሆኔታዎች አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ፣የኤች አይቪ /ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር የትኩረት አቅጣጫዎች እና ምን መደረግ አለበት በሚሉ ርዕሶች ላይ ስልጠናው ያተኮረ መሆኑን ተናግረዋል።

 

0 Comments

Submit a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

SITE VISITORS

  • 0
  • 66
  • 44
  • 2,771
  • 8,458
  • 238,504
  • 238,504