ዜና

በአዲስ አበባ ከተማ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እና ተቋማት ዕውቅና ተሰጠ።
(መስከረም 27/2017 ዓ.ም) በመርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ፣የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ እና የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶክተር ብርሀነ መስቀል ጠናን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት አመራሮች፣ባለሙያዎች እንዲሁም ተሸላሚ ተማሪዎች እና ወላጆቻቸው የተገኙ ሲሆን ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ላፕቶፕና ታብሌቶችን ጨምሮ የተለያዩ...

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የኢሬቻ በአልን አስመልክቶ የፓናል ውይይት አካሄደ።
(መስከረም 23/2017 ዓ.ም) የፓናል ውይይቱ "ኢሬቻ ለባህላችን ህዳሴ" በሚል መሪ ቃል በሽማግሌዎች ምርቃት የተጀመረ ሲሆን በመርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የማኔጅመንት አባላትን ጨምሮ አጠቃላይ ሰራተኞችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በመርሀ ግብሩ መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት የኢሬቻ በአል...

ልሳነ ብዙህነት ለሁለንተናዊ ስኬት ላቅ ያለ ሚና እንዳለው ተገለጸ፡፡
(መስከረም 22/2017 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ሰልጠና የወሰዱ የቢሮው ሰራተኞች በዛሬው እለት የተመረቁ ሲሆን በምረቃ መርሀ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ፣ የቢሮ ማኔጅመንት አባላት ፣ የቢሮ ሰራተኞችና ስልጠናዉን የሰጡ መምህራን ተገኝተዋል፡፡ ስነ ስርዓቱ በሽማግሌዎች ምርቃት የተጀመረ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ...

በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተካሄደ የድጋፍና ክትትል ግብረ መልስ ዙሪያ በየደረጃው ከሚገኙ ሱፐርቫይዘሮች ጋር ውይይት ተካሄደ።
(መስከረም 22/2017 ዓ.ም) ድጋፍና ክትትሉ በ2016 ዓ.ም የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ተግባራዊ አድርገው ትራንስፎርም እንዲሆኑ በተለዩ 40 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በተመሳሳይ ለ2017 ዓ.ም በተለዩ 60 ተቋማት የተካሄደ ሲሆን ግብረ መልሱ በቢሮው የቀዳማይ ልጅነት ጉዳዮች ቡድን መሪ ወይዘሮ ፍሬሕይወት በቀለ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ...

ከኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ጋር ለመምህራን የጋራ መኖሪያ ቤት ለመገንባት የሚያስችል የመጀመሪያ ዙር የብድር ውል ስምምነት ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ::
(መስከረም 21/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የመኖሪያ ቤት የሌላቸው መምህራን ተደራጅተው የቤት ባለቤት እንዲሆኑ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ በዛሬው እለትም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ፣ የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር እና የአዲስ አበባ ህብረት ሥራ ኮሚሽን ከኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ጋር ለመምህራን የጋራ ቤት ለመገንባት በሚያስችል የብድር ውል ስምምነት...

ከሀብት ምዝገባ ጋር በተያያዘ የሚታዩ የአረዳድ ክፍተቶችን ለማስተካከል የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ::
(መስከረም 20/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮው የስነ ምግባርና ፀረ -ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት በሀብት ማስመዝገብ ላይ ያተኮረ ስልጠና ለቢሮው አጠቃላይ ሰራተኞች ሰጥቷል :: ቀደም ሲል በሀብት ማስመዝገብ ላይ ግንዛቤ መፍጠር ሥራ መሰራቱን ያስታወሱት የቢሮው የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክተር አቶ አስራት ሽፈራው አሁን እየተካሄደ ካለ ሀብት ማስመዝገብ ጋር በተያያዘ አንዳንድ...

ለአካቶ ትምህርት ውጤታማነት በትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ፡፡
(መስከረም 20/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ በፊት የሚያዘጋጀው የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት የተካሄደ ሲሆን በመድረኩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ፣ የቢሮ ማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል። በመርሀ ግብሩ በአካቶ ትምህርት ጽንሰ ሀሳብ ላይ መሰረት ያደረግ ሰነድ በአቶ...

የአዲስ አበባ ከተማ የ2017 የትምህርት ዘመን ትምህርት አጀማመር ተገመገመ፡፡
(መስከረም 10/2017 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 የትምህርት ዘመን ትምህርት መሰከረም 6/ 2017 ዓ.ም መጀመሩን ተከትሎ የትምህርት አጀማመሩን አስመልከቶ ግምገማ ተካሂዳል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊና የቢሮ ሀላፊ ተወካይ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የ2017 የትምህርት ዘመን ትምህርት በከተማ አስተዳደሩ በድምቀት መጀመሩን በመጥቀስ አጀማመሩን አስመልክቶ በተካሄደ...

በመስቀል ደመራ እና ኢሬቻ በአላት አከባበር ዙሪያ አጠቃላይ ሰራተኞች በተገኙበት ውይይት ተካሄደ።
(መስከረም 9/2017 ዓ.ም) ውይይቱ የአብሮነት ፣ የወንድማማችነት/የእህታማማቾች የፍቅር መገለጫ የሆኑ በዓላቶችን በጋራ እናክብር! በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን በመርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አበበ ቸርነት የ2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ እና ኢሬቻ በአላት አከባበርን በተመለከተ የተዘጋጀ ሰነድ አቅርበው ውይይት ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ...

በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተካሄደ የድጋፍና ክትትል ግብረ መልስ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።
(መስከረም 9/2017 ዓ.ም) በውይይቱ በ2016 ዓ.ም የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ተግባራዊ አድርገው ትራንስፎርም እንዲሆኑ የግብአት ድጋፍ ከተደረገላቸው 40 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በ2017 ዓ.ም ፕሮግራሙ ተግባራዊ ከሚደረግባቸው 60 ተቋማት የተውጣጡ ርዕሳነ መምህራን እና አስተባባሪዎችን ጨምሮ የክፍለ ከተማ የዘርፉ አስተባባሪዎች እና ቡድን መሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር...