(ቀን 6/2/2016 ዓ.ም) በ2015 ት/ት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ለይ በአካል በመምጣት ቅሬታ ላቀረቡ በስልክ ወይም በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ምላሽ መሰጠቱንና እየተሰጠ መሆኑን የት/ት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጻል።
በበይነ መረብ(Online) ቅሬታ ላቀረቡም ምላሹ በበይነ መረብ የተሰጠ እንደሆነ እና ከዚህ በፊት ውጤት በታየበት መልኩ በድረ ገጽ eaes.et ላይ ምላሹን ማየት የሚቻል መሆኑን አሳውቃል።
በቁጥር የተወሰኑ ቅሬታዎች በምላሽ ሂደት ላይ ያሉ በመሆኑ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን ሲል የት/ት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቃል።
0 Comments