(አዲስ አበባ 24/1/2016 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ጋር በመሆን የአፍሪካ ከንቲባዎች የሊደርሺፕ ኢኒሼቲቭ (AMALI)ተ ሳታፊዎችን አፍሪካ አንድነት ቁጥር 2 የቅድመ አንደኛ ደረጃ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን አስጎበኙ።
ጉብኝቱ በዋናነት በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቀዳማይ ልጅነት ፕሮጀክት አተገባበር ምንደረጃ ላይ እንደሚገኝ በማየት ፕሮግራሙን በቀጣይነት ለመደገፍ እንዲቻል ታስቦ የተካሄደ ሲሆን የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ በመዘዋወር የህጻናቱን የመማሪያ ፣ የመጫወቻ እና የማሸለቢያ ክፍሎች ጎብኝተዋል።
0 Comments