የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘርፈ ብዙና ቀዳማይ ልጅነት ጉዳዮች ትግበራ ዳይሬክቶሬት ስልጠና ሰጠ ::

by | ዜና

(አዲስ አበባ 22/1/2016 ዓ.ም)   ስልጠናውን በውይይት ያስጀመሩት የኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ባለሙያ ገንዘብ ደሳለኝ እንዳሉት ከዚህ በፊት በመንግስት ፣ በተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች በተደረገ ርብርብ የኤች አይ ቪ ስርጭት ቀንሶ እንደነበር አስታውሰው መዘናጋቱ በዚሁ ከቀጠለ ካለፈው ጊዜ በባሰ ሁኔታ ሀገራችንን ዋጋ ያስከፍላል ብለዋል :: የኤች አይ ቪ ስርጭት ምጣኔ በ 2023  ዜሮ ለማድረስ ቢታቀድም በታቀደው ልክ መስራት እንዳልተቻለ ያብራሩት ባለሙያዋ በማስተዋልና የኤች አይ ቪ ጉዳይን በሥራችን እያካተትን በመስራት ሰራተኞችን በማወያየት ስርጭቱን ለመቀነስ ጥረት መደረግ አለበት ብለዋል ::

ስልጠናው የኤች አይ ቪ ኤድስ ቁልፍ እውነታዎች በሚል ርዕስ  ከጤና ጥበቃ ሚንስትር በመጡ አቶ መኮንን የተሰጠ ሲሆን የኤች አይ ቪ አሁናዊ መረጃ በዓለምና በኢትዮጵያ እንዲሁም ከተማችን በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ ውይይት ተደርጓል::  አቶ መኮንን በስልጠናው ወቅት ኤች አይ ቪ ከገጠር ይልቅ በከተማ ያለው ስርጭት ሰፊ መሆኑን አውስተው እንደ አዲስ አበባ አሁንም የኤች አይ ቪ ስርጭት አሳሳቢ መሆኑን በመረዳት ቅንጅታዊ አሰራርን በማስፈን ሁሉም በእኔነት ስሜት እንዲሰራ ማድረግና የድጋፍና ክብካቤ ስራን ማጠናከር እንዲሁም ሜንስትሪሚንግ ላይ ጠንክሮ በመስራት ሥርጭቱን መግታት አለብን ብለዋል :: አያይዘውም ቢሮዎች ሁሉንም ሰራተኞች በኤድስ ፈንድ ላይ በማሳተፍና የኤች አይ ቪ ሴክተር ሜንስትሪሚንግን በማበረታታት አምራች የሆነውን የሰው ኃይልን በመጠበቅ ኤች አይ ቪን መቆጣጠር መቻል አለባቸው ብለዋል ::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ወ /ሮ ታጋይቱ አባቡ በስልጠናው መዝጊያ ላይ በመገኝት ባስተላለፉት መልዕክት ሰራተኛው በስልጠናው የተላለፈውን መልእክት ችላ ሳይል የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት እንዳይስፋፋ ራሱንና ቤተሰቡን መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል ::

የቢሮው አዳዲስ ሰራተኞችም የኤድስ ፈንድን በመቀላቀል ድጋፍ ለሚፈልጉ ህፃናትና በኤች አይ ቪ የተጎዱ ወገኖችን እንዲያግዙ ጥሪ ቀርቧል ድጋፍም ተሰጥቷል::

0 Comments

Submit a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

SITE VISITORS

  • 0
  • 0
  • 205
  • 6,046
  • 31,180
  • 147,475
  • 147,475