የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የደጋፊ ሥራ ሒደቶች ዘርፍ የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ተገመገመ ::

by | ዜና

(ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም) በዘርፉ የሚገኙ ዳይሬክቶሬቶች በስድስት ወራት ውስጥ በዋናነት ተቆጥረው የተሰጡ ተግባራትን ጥራቱንና የተቀመጠለትን ወቅት በጠበቀ መልኩ እንዲሁም የተቋሙን አገልግሎት ከማሻሻል አንፃር የተከናወኑ ሥራዎች አቅርበው ግምገማ ተካሄዳል::

             

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ በተቋሙ የሚገኙ ዳይሬክቶሬቶች የጋራ ውይይት ማድረጋቸው አንዱ ከአንዱ አፈፃፀም የተሻሉ ተሞክሮዎችን በመውሰድ የተሻለ አፈፃፀም እንዲያሳዩ ያደርጋል ብለዋል:: ለተቋሙ ስኬትም ከአገልግሎት አሰጣጥና ሥራዎችን ተናቦ ከመስራት አንፃር የሄዱበትን ርቀት በማስጠበቅ ለተሻለ ውጤት ከባለሙያዎች ፣ ቡድን መሪዎችና ዳይሬክቶሬቶች ቀጣይ ሰፊ ሥራ እንደሚጠበቅ አብራርተዋል:: አያይዘውም እያንዳንዱ የስራ ክፍል ተመሳሳይ የስራ አፈፃፀም እንዲኖረው ፣ የተከናወኑ መረጃዎችን በአግባቡ መሰነድና ስራን ከቀደመው የበለጠ በተነሳሽነት ስሜት ለመፈፀም እቅዶችን ከልሶ ወደተግባር መግባት እንደሚጠበቅ አሳስበዋል ::

               

ዳይሬክቶሬቶቹ በስድስት ወራት ያከናወኗቸውን ተግባራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርቶች አቅርበው ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል ::

0 Comments