የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ያለበት ደረጃን በተመለከተ ግምገማ ተካሄደ፡፡

by | ዜና

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 11 ፣ 2015 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ)  በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሁሉም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ የ1ኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ እየተካሄዱ የሚገኘው የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ  ሥራዎች ያሉበት ደረጃ ተገመገመ ::

በግምገማው በሁሉም ክፍለከተሞች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከሀብት አሰባሰብና  የተሰበሰቡ ሀብቶችን ተገቢ ቦታ ላይ ከማዋል አንፃር የተሰሩ ስራዎች እንዲሁም ቀድሞ በእጥረት ይታዩ የነበሩና አሁን በተገኝ ሀብት የተሰጡ  መፍትሄዎች  ቀርበዋል ::

የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሻሻልና ለትምህርት አሰጣጥ ምቹ ለማድረግ ትምህርት ለትውልድ በሚል ስያሜ  የተጀመረውን ንቅናቄ በስኬት ለማጠናቀቅ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣  ህብረተሰቡን በማሳተፍ ፣ ከግል ባለሀብትና ግብረሰናይ ድርጅቶች በተገኙ የቁሳቁስና የጉልበትድጋፎች  የመማሪያ ክፍሎች ግንባታና እድሳት፤   የምድረ ግቢ ማስዋብና እድሳት እንዲሁም የትምህርት ስራውን ለማገዝ የሚረዱ በርካታ ተግባሮች እየተሰሩ መሆኑ ተብራርቷል ::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ወንድሙ ዑመር  በሁሉም ክፍለ ከተሞች ያሉ የስራ ሪፖርቶች ይዘት ስራው ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን እንደሚያመላክት ገልፀዋል :: አቶ ወንድሙ አያይዘውም የንቅናቄ ስራው በሚዲያ  እንዲደገፍ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበዋል ::

0 Comments

Submit a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

SITE VISITORS

  • 0
  • 311
  • 374
  • 4,292
  • 15,622
  • 98,488
  • 98,488