“ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ” በሚል የሚናፈሰው ወሬ ከእውነት የራቀ ነዉ፡፡

by | ዜና

ቀን 16/9/2014 ዓ.ም

“ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ” በሚል የሚናፈሰው ወሬ ከእውነት የራቀ ነዉ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2014 የትምህርት ዘመን በከተማዉ የሚሰጠዉ ትምህርት ውጤታማ እንዲሆን ዘርፈ ብዙ ተግባራት በመከናወን ላይ የሚገኙ ሲሆን በዚህ ሂደት ውስጥ መምህራን ፣ ተማሪዎች ፣ ወላጆች ፣ የትምህርት ባለሙያዎች እና አመራሮች ፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ከምንጊዜውም በላይ የትምህርት ጥራት ፣ ተደራሽነት ፣ ተገቢነት እና ፍትሃዊነት እንዲረጋገጥ የበኩላቸዉን ሚና በመወጣት ላይ በመሆናቸዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምስጋናዉን ያቀርባል፡፡

በ2014 የትምህርት ዘመን ማጠቃለያ ላይ ተማሪዎች ለትምህርታቸዉ ትኩረት ሰጥተዉ ከክፍል ክፍለ መዘዋወሪያ ማጠቃለያ ፈተናዎችን ለመውስድ እየተዘጋጁበት ባለበት ወቅት ላይ ማህበራዊ ሀላፊነት በጎደላቸው አካላት ሆን ተብሎ ተማሪዎችን ለማዘናጋት በዘንድሮ ዓመት ከክፍል ወደ ክፍል መዘዋወር የለም ተብሎ በማህበራዊ ምህዳሮች የሚናፈሰው ወሬ ፍፁም ከእውነት የራቀ እንዲሁም ከዚህ ጋር በተያያዘ ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የወረደ አቅጣጫ የሌለ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እያሳወቀ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተማሪዎች “ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ” በሚል አሉባልታ ሳይጠለፉ እና ሳይምታቱ ለትምህርታቸው ትኩረት ስጥተዉ ለተሻለ ውጤት እንዲተጉ እንድታደርጉ አደራ እንላለን፡፡

0 Comments

Submit a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

SITE VISITORS

  • 0
  • 205
  • 158
  • 7,078
  • 31,331
  • 147,475
  • 147,475