ሁለንተናዊ ርብርብ ለትምህርት ተቋማት ” በሚል መሪ ቃል ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ 30ኛው ከተማ አቀፍ የትምህርት ጉባኤ በጀት አመቱን በስኬት ላጠናቀቁ አካላት እውቅና በመስጠት ተጠናቀቀ ።

by | ዜና

አዲስ አበባ ነሀሴ 19 /2015 ዓ.ም   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በጉባኤው መዝጊያ ለመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች ባስተላለፉት መልእክት የእውቅና ስነ-ስርዓቱ  በተማሪዎች መካከል ጤናማ ፉክክር የሚፈጥር የሽልማት ስነ-ስርዓት መሆኑን ገልፀው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የነገ የኢትዮጵያ ተስፋ ለሆኑ ተማሪዎች ምስጋና አቅርበዋል ።

በ2016 የትምህርት ዘመንም የተማሪን ስነ-ምግባርና ውጤት በማሻሻል የሚፈለገው ደረጃ ላይ ለማድረስና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ሙሉ ጊዜያችሁን በመስጠት ለትምህርት ሥራ ስኬታማነት በጋራና በቅንጅት መስራት ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ይጠበቃል ሲሉ አሳስበዋል :: ዶክተር ዘላለም አያይዘውም በ31ኛው የትምህርት ጉባኤ ከዚህ የተሻለ የአሰራር ስርዓትና ውጤት የምናስመዘግብበት እንደሚሆን እምነት አለኝ ብለዋል ::

በእለቱም የበጀት ዓመቱን ትምህርት ሥራ ስኬታማ ለማድረግ በተደረጉ እንቅስቃሴዎች ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላደረጉ ማለትም አዲሱን ስርአተ ትምህርት በሬድዮ እንዲቀረፅ ላደረጉ የተቋሙ ሰራተኞች ፣ በዘንድሮ የ6ኛና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶችና ተማሪዎች ፣ ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ማየትና መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎችና ትምህርት ፅህፈት ቤቶች እንዲሁም በሥራ አፈፃፀም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አላማ ፈፃሚና ደጋፊ ዳይሬክቶሬቶች የእውቅናና ማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል ::

0 Comments

Submit a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

SITE VISITORS

  • 0
  • 311
  • 374
  • 4,292
  • 15,622
  • 98,488
  • 98,488